Skip Navigation Links    
     





 

 
የደረቅ ወደብ አገልግሎት ደርጅት በሞጆ የሰባት ሄክታር ኮንቴይነር ማስተናገጃ ተርሚናል ለማስገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ

Thursday, July 29, 2010

 
     
   

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22 2002 (ሬዲዮ ፋና) የደረቅ ወደብ አገልግሎት ደርጅት በሞጆ ደረቅ ወደብ የሰባት ሄክታር ኮንቴይነር ማስተናገጃ ተርሚናል ለማስገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

 

ድርጅቱ ስምምነቱን የተፈራረመው ግንባታውን ከሚያካሄደው ከውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ነው።

 

          ስምምነቱን የተፈራረሙት በደረቅ ወደብ አገልግሎት ድርጅት በኩል ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ እውነቱ ታዬ እና የውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አበበ አየነው ናቸው፡፡

 

          ግንባታው የሚካሄደው ከ254 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሆነ የባልደረባችን ታደሰ ብዙአለም ዘገባ ያመለክታል ፡፡

 

          ግንባታው ሲጠናቀቅም የሞጆ ደረቅ ወደብ በዓመት የሚያስተናግደውን 28 ሺ 280 ኮንቴይነር ወደ 110 ሺ 373 ከፍ ያደርገዋል፡፡

 

 

 
     
 
Other Stories

የምንዛሬ ተመን ማስተካከያው የተጀመረውን ዕድገት ለማስቀጠል ይረዳል ተባለ

የመረጃ ነጻነት ህግ አገራዊ ተፈጻሚነት እንዲኖረው ነጻ በሆነ መልኩ መፈጸም ይኖርበታል ተባለ

የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጡ የወጪ ንግድን ለማጠናከር ይረዳል --- የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

አዲሱ የከፍተኛ ትምህርት መመሪያ ጥራትን ለማረጋገጥ የተቀረፀ መሆኑ ተጠቆመ

የታዳሽ ኃይል ዘርፍ ጥቅምን ለማረጋገጥ ፕሮጀክት ተዘጋጀ

ኮርፖሬሽኑ ሰሞኑን "አደገኛ የሞባይል ፍሪኩዌንሲ በጤና ላይ አደጋ ያደርሳል" ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ መሆኑን አስታወቀ

ለህጻናት የፓርላማ አባላት ስልጠና እየተሰጠ ነው

አምስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች የኢትዮጵያ የላቦራቶሪ ማህበርን ሊመሰርቱ ነው

ያልተመዘገቡ የበጎ አድራጎት ደርጅቶችና ማህበራት የያዟቸውን ንብረቶች እንዲያስረክቡ ሊደረግ ነው

በፌዴራሊዝም ስርዓት ዙሪያ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ ነው