አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22 2002 (ሬዲዮ ፋና) ሀገራችን ከሁለት ሳምንት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አህጉራዊ ጉባኤን ታስተናግዳለች።
ጉባኤው በመጪው ነሃሴ ወር መጀመሪያ ላይ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል።
ይኸው ጉባኤ በሀገራችን ብሎም አፍሪካ የተሟላ የውልደትና የሞት የምዝገባ ስርአት መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል።
የማእከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጄንሲ ጉባኤውን አስመልክቶ ዛሬ በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱን የባልደረባችን አምሳለ ተስፋዬ ዘገባ ያመለክታል።