Skip Navigation Links    
     





 

 
በህገ ወጥ ኤጄንሲዎች ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ

Thursday, July 29, 2010

 
     
   

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22 2002 (ሬዲዮ ፋና) የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በህገ ወጥ ኤጄንሲዎች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታወቀ።

 

የሰዎች ህገ ወጥ ዝወውር እንደማንኛውም ህገ ወጥ ድርጊት ተቆጥሮ ጠንካራ አቋም መያዙንና  በህገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱትን ለመገደብም በአዋጁ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ መጀመሩን በሚኒስቴሩ የስራ ስምሪት አገልግሎት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ሃይሌ ገልጸዋል።

 

 

የግንዛቤ ማስጨበጫ የተለያዮ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነና ከህጋዊ ኤጄንሲዎች ጋር በመተባበር ለችግሩ መፍትሄ የሚሆን ተግባር በመከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመው ኤጄንሲዎች ህግን አክብረው እንዲሰሩ ጥረት መደረጉንም አብራርተዋል።

 

     

 

 ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገር  ኤጄንሲዎች ጋር ተባብሮ በመስራት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንና ችግሩን በዘላቂነት ለማስቆምም የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተካሄደ መሆኑም ተመልክቷል።

 

 እስካሁን ድረስም 54 ኤጀንሲዎች በህጋዊነት ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን የባልደረባችን እመርታ አስፋው ዘገባ ያመለክታል።

 
     
 
Other Stories

የምንዛሬ ተመን ማስተካከያው የተጀመረውን ዕድገት ለማስቀጠል ይረዳል ተባለ

የመረጃ ነጻነት ህግ አገራዊ ተፈጻሚነት እንዲኖረው ነጻ በሆነ መልኩ መፈጸም ይኖርበታል ተባለ

የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጡ የወጪ ንግድን ለማጠናከር ይረዳል --- የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

አዲሱ የከፍተኛ ትምህርት መመሪያ ጥራትን ለማረጋገጥ የተቀረፀ መሆኑ ተጠቆመ

የታዳሽ ኃይል ዘርፍ ጥቅምን ለማረጋገጥ ፕሮጀክት ተዘጋጀ

ኮርፖሬሽኑ ሰሞኑን "አደገኛ የሞባይል ፍሪኩዌንሲ በጤና ላይ አደጋ ያደርሳል" ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ መሆኑን አስታወቀ

ለህጻናት የፓርላማ አባላት ስልጠና እየተሰጠ ነው

አምስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች የኢትዮጵያ የላቦራቶሪ ማህበርን ሊመሰርቱ ነው

ያልተመዘገቡ የበጎ አድራጎት ደርጅቶችና ማህበራት የያዟቸውን ንብረቶች እንዲያስረክቡ ሊደረግ ነው

በፌዴራሊዝም ስርዓት ዙሪያ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ ነው