አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21 2002 (ሬዲዮ ፋና) የአለም የኤች አይ ቪ ኤድስ የጋራ ፕሮግራም ኢትዮጽያ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ያደረገችውን እንቅስቃሴ አደነቀ።
የአለም የኤች አይ ቪ ኤድስ የጋራ ፕሮግራም ዋና ሃላፊ ሚስተር ሚቼል ሲዲቤ በኢትዮጽያ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው።
የጉብኝቱ አላማም ኢትዮጽያ ከሌሎች ሃገራት ጋር የገባቻቸውን ውሎች ተግባራዊ ማድረጓን ለማረጋገጥ እና የምእተ አመቱን ግብ ለማሳካት መደረግ ባለበት ጉዳይ ላይ ለመምከር ነው።
የኢትዮጽያ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ዕህፈት ቤት ያከናወናቸውን ተግባራት ሪፖርት ያደመጡት ሃላፊው ሃገሪቱ ስርጭቱን ለመግታት በተለይም ህብረተሰብ ተኮር በሆነ የመከላከል ተግባር ላይ ያደረገችውን እንቅስቃሴ አድንቀዋል ።
በቀጣይም ዕህፈት ቤታቸው በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ዋና ሃላፊው በቀጣይም የጳውሎስን ሆስፒታል ጨምሮ ሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችንም ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።